ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የ ‹‹ሰማያዊ›› ፓርቲ ሊቀመንበር ከላይፍ መጽሄት ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ

ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የ ‹‹ሰማያዊ›› ፓርቲ ሊቀመንበር ናቸው፡፡ ፓርቲው ከተመሰረተ ጥቂት እድሜ ያስቆጠረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሚነሳ ለመሆን በቅቷል፡፡ የላይፍ መጽሄት አዘጋጅ የሆነው ዳዊት ሰለሞን ግንፍሌ አካባቢ በሚገኘው የፓርቲው ጽ/ ቤት በመገኘት ኢንጅነሩን በዋናነት ስለ አማሮች መፈናቀል አነጋግሯቸዋል፡፡

ሰላማዊ ትግላችንን ከፍ አድርገን እንቀጥላለን!!!

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

ሰማያዊ ፓርቲ በተለያዩ ጊዚያት በሐገራችን የሚፈፀሙ የተለያዩ የሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶችና ህገ ወጥ ድርጊቶች ኢንዲቆሙ ለመንግስት የተለያዩ ጥያቄዎችን ሲያቀርብ ቢቆይም ከመንግስት የተሰጡት ምላሾች ግን ጥያቄዎቻችንን ማንቋሸሽና ማጣጣል ወይም ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ማለፍ ሆኖ ቆይቷል፡፡

የኢትጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድና ገዢው ፓርቲ/መንግሥት ተገደው እንዲሰሙ የማድረግ ህዝባዊ ትግል ይቀጥላል!!

ጥያቄዎቻችን በ “ጆሮ ዳባ ልበስ” ሊታለፉ አይገባም፤ የኢትጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድና ገዢው ፓርቲ/መንግሥት ተገደው እንዲሰሙ የማድረግ ህዝባዊ ትግል ይቀጥላል!!
ከ33 ቱ የፔቲሽን ፈራሚ ፓርቲዎች ባቀረብነው ጥያቄ ዙሪያ በቀጣይ የጋራ አቋም ላይ የተሰጠ መግለጫ

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ ጥር 3 ቀን 2005ዓ.ም

ሰማያዊ ፓርቲ ሕዝባዊ ውይይት አካሄደ "ለኢትዮጵያ የሚያስፈልገው ሕዳሴ ሳይሆን አብርሆት ነው" አቶ አበባው አያሌው በአ.አ.ዩ የታሪክ መምህርና ተመራማሪ

የፖለቲካ ትግልን የጥቂት ፖለቲከኞች ጉዳይ ከማድረግ ይልቅ ትግሉን ወደሕዝቡ ማውረድና ትግሉ በፖለቲካ መድረክ ላይ ብቻ ሳይሆን በሕብረተሰቡ ውስጥ መካሄድ ያለበት መሆኑን የጠቀሱት አቶ አበባው ይህ ሊሆን የሚችለው አብርሆትን በመፍጠር ነው! አብርሆት የሚፈጠረው ደገሞ ልሂቃንን፣ ሚዲያውንና ስነጥበብን በማንቀሳቀስ ጭምር መሆኑን ገልፀዋል፡፡

“ለዘለቄታዊ የስርዐት ግንባታ አዲስ የፖለቲካ ባህል በኢትዮጵያ”

በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት
“ለዘለቄታዊ የስርዐት ግንባታ አዲስ የፖለቲካ ባህል በኢትዮጵያ”
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና ተመራማሪ በሆነው አቶ አበባው አያሌው አቅራቢነት
በፕሮግራሙ ላይ
ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም
ኢ/ር ኃይሉ ሻወል
ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ
ፕ/ር ገብሩ ታረቀኝ
ፐ/ር በፍቃዱ ደግፌ
ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም
ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ
አርቲስት ደበበ እሸቱ
በተጋባዥ እንግድነት ይገኛሉ::
በ 14/04/2005 ኣ.ም እሁድ 3 ሰዓት ላይ ግንፍሌ አካባቢ በሚገኘው የፓርቲው ፅ/ቤት
ግንፍሌ እርካታ ሆቴል ፌት ለፊት

እሁድ ታህሳስ 14 ቀን 2005 ዓ/ም

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

የሁለት ዓለማቱ መለስና ኢህአዴግ (በኤልያስ ገብሩ)

(ዓለም ፩ - መለስ ዘሀሎ)
- ግንባሩ ኢህአዴግ ወይስ መለስ?
- “ጀግንነት” አይሞትም በሉ
(ዓለም ፪ - መለስ ዘአልቦ)
- አቶ መለስ ይረፉበት፣ ጠ/ሚ/ር ኃይለማርያምን እንጠንቀቃቸው!
- መለስን የመምሰል አባዜ (ከሺህ ምላስ አንድ መለስ!)
- የብዙ ማንነቶች ባለቤት - መለስ
- መረጋጋት እና ወደ ልቦና መመለስ
- አቶ ኃይለማርያም፣ ራስዎትን ይሁኑ!
-

‹‹አሜሪካ የመጣሁት ከቃሊቲ ስለሚሻል ብቻ ነው›› ዳዊት ከበደ (የቀድሞው የአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ማኔጂንግ ኤዲተር)

በ97 ዓ/ም. በሀገራችን ተከስቶ በነበረው ፖለቲካዊ ቀውስ ሣቢያ ለእስር ከተዳረጉ ጋዜጠኞች መካከል አንዱ ነው፡፡ ከአንድ ዓመት ከዘጠኝ ወራት እስር በኋላ በሂደት አውራምባ ታይምስ ጋዜጣን በየካቲት ወር 2ዐዐዐ ዓ.ም. አቋቁሞ ማሳተም ጀመረ፡፡ የሲፒጄ የ2ዐ1ዐ የኘሬስ ነፃነት ዓለም አቀፍ ተሸላሚ የነበረው - ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ፡፡ ህዳር 9 ቀን 2ዐዐ3 ዓ/ም. ግን “ይቅርታዬ ተነስቶ እንድታሠር በመወሰኑ ከፍትህ ሚኒስቴር አስተማማኝ ምንጭ መረጃ አገኘሁ” በማለት ከሀገሩ ወደ አሜሪካ መሰደዱ ይታወሳል፡፡
ኤልያስ ገብሩም ለቀድሞው የአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ማኔጂንግ ኤዲተር ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ በተለያዩ ርዕሠ ጉዳዮች ዙሪያ ጥያቄ በማንሣት ተከታዩን ቃለ-ምልልስ አድርጓል፡፡

Pages

Subscribe to ሰማያዊ ፓርቲ RSS