Submitted by Admin on Fri, 12/07/2012 - 15:15
ሰልፉ የት ይደርሳል?
በኤልያስ ገብሩ
ወጣት ናሆም አለሙ የአዲስ ከተማ ነዋሪ ነው፡፡ ከሳምንታት በፊት አንድ ጓደኛውን መንገድ ላይ ያገኘዋል፡፡ ጓደኛውም ናሆምን “የምትኖረው የት ነው?” የሚል ጥያቄ ያቀርብለትና ናሆምም አካባቢውን ይናገራል፡፡ ወዲያው ጓደኛው፣ “አንድ ሠፈር ነው የምንኖረው፡፡ እኔም እዚሁ አካባቢ ሆኛለሁ፡፡ በቃ ችግር የለም፡፡ ከእንግዲህ እንደልብ እንገናኛለን” በማለት መልስ ይሰጣል፡፡ ናሆምም ”እንዴት?” በማለት በአግራሞት ድጋሚ ጥያቄ ያነሳል፡፡ “እንደልብ የምንገናኘው ታክሲ ወረፋ ስንጠብቅ ነዋ!” የሚል መልስ ከጓደኛው ያገኛል፡፡ ናሆምም ጉዳዩን ጊዜ ሰጥቶ ካሰበ በኋላ ለረዥም ጊዜ ሳያገኛቸው የኖሩ ጓደኞቹን የታክሲ ሰልፍ እያገናኘው መሆኑን ለዚህ ፅሁፍ አዘጋጅ በምፀት አስረድቷል፡፡ ……………
Submitted by Admin on Fri, 12/07/2012 - 15:00
ኘ/ር ዓለማየሁ ገ/ማሪያም አሜሪካን አገር በካሊፎርኒያ ስቴት ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ ኘ/ር እና የህግ ጠበቃ ናቸው፡፡ ኘ/ሩ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብትና የዲሞክራሲ ጉዳዮች ላይ በየሳምንቱ በመፃፍ ይታወቃሉ፡፡ በተለይም ከምርጫ 97 ጋር ተያይዞ በአሜሪካ መንግሥት ፓርላማ HR2003 የተባለውን የኢትዮጵያ መንግሥት ግልፅነትና ተጠያቂነት በተመለከተ የህግ ረቂቅ እንዲዘጋጅና ለም/ቤት እንዲቀርብ ሰፊ ጥረት በማድረግ ይታወቃሉ፡፡
የሰማያዊ መፅሔት ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ አናንያ ሶሪ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከኘ/ሩ ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ እናቀርባለን፡፡
Submitted by Admin on Fri, 11/02/2012 - 15:18
በቅድሚያ ጽሁፉን አንብበህ ጨርስና ከዚያ በኋላ የራስህን/የራስሽን አቋም ትወስዳለህ፡፡ ጽሁፉን በሙሉ ሳታነብ ግን ቸኩለህ አትደምድም፡፡ ከስህተት ላይ ትወድቃለህና! የጅብ ችኩል ቀንድ ይነክሳልና! የብዙዎቻችን ችግርስ ምን ሆነና?! ይኸው በወሬ እና በስሚ- ስሚ እየተፈታን ብሎም እየተነዳን አይደለ እንዴ በዘመናችን ሁሉ የተቀለደብን?! ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው! እንዲል ተረቱ፡ ፡ ስለዚህ “አንድን መጽሐፍ በሽፋኑ ብቻ አትፍረደው!” /Never Judge a book by its cover/ እንደሚባለው የፈረንጆቹ አባባል በርዕሱ ብቻ ተመርተህ የጽሑፉን ጭብጥ እንዳገኘኸው ሆኖ አይሰማህ፡፡ ርዕሱ ቁንጽል ሀይለ-ቃል ብቻ ነው፡፡ ቁም- ነገሩን በዝርዝሩ ውስጥ ነው የምታገኘው፡ ፡
Submitted by Admin on Fri, 11/02/2012 - 14:24
በአብዛኛው በወጣቶች የተቋቋመው ሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በተለያዩ ሃገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከሰማያዊ ፓርቲ ድረ-ገጽ ጋር ያደረጉት ቃለ-ምልልስ እጅግ አንኳርና አንገብጋቢ ነጥቦችን ይዞ ቀርቧል፡፡ እኛም እነሆ ብለናል፡-
Submitted by Admin on Tue, 10/30/2012 - 14:23
ሰማያዊ ሚዲያ በመጪው ረቡዕ ገበያ ላይ ትውላላች (ቅጽ 1 ቁጥር 1 ጥቅምት 2005ዓ.ም )
Submitted by Admin on Tue, 10/16/2012 - 14:50
ኢማ ጎልድማንና አሌክሳንደር በርክማን የአሜሪካን አናርኪስት እንቅስቃሴ መስራችና የድርጅታቸው ልሳን የሆነው የወርሃዊ ዕትም ማዘር ርዝ የተሰኘው መፅሔት አዘጋጆች ነበሩ፡፡ ኢማ እና ጓደኛዋ በአንደኛው የዓለም ጦርነት በአሜሪካን የወጣውን የወታደራዊ ግዴታ ረቂቅ አዋጅ ወጣት ወንዶች እንዲቃወሙ የሚቀሰቅስ ማንፌስቶ በማሰራጨታቸው የአሜሪካንን የዘመቻ ህግ በመጣስ ሴራ ተከሰው ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅና አምባገነኖችን የመቃወም መብቶች እንዲከበሩ እ.ኤ.አ በሰኔ 1917 ኢማ በችሎቱ ፊት ቀርባ ያደረገችውን ንግግር ለዛሬው ትውልድና ለሰላማዊ ታጋዮች የሚያስተምን ነገር አለ ብዬ ስላመንኩ ትርጉሙን እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ፡፡ መልካም ንባብ!!!
አዘጋጅ፡- ኢማ ጎልድማን
ትርጉም፡- ወረታው ዋሴ
woretawwassie@gmail.com)
Submitted by Admin on Mon, 10/15/2012 - 08:56
በብሄራዊ ቡድናችን ውጤት ሰማያዊ ፓርቲ የተሰማውን ደስታ እየገለጸ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እኳን ደስ ያላችሁ ይላል!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
Submitted by Admin on Thu, 08/16/2012 - 16:07
በመጪው እሁድ ነሐሴ 13 ቀን 2004 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት “የኢትዮጵያ ፖለቲካ ስለ አዎንታዊ ለውጥ” በሚለ ርዕስ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ትምህርት ክፍል መምህር በሆኑት በአቶ አበባው አያሌው ፅሁፍ አቅራቢነት ውይይት ይካሄዳል።
አቶ አበባው አያሌው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የታሪክና የስነ-ጥበብ ታሪክ መምህር ሲሆኑ በሰሜንና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ላይ የተለያዩ ጥናቶች በማድረግና ደፈር ያሉ ፖለቲካዊ አስተያየቶችን በመፃፍ ይታወቃሉ።
Submitted by Admin on Fri, 07/27/2012 - 09:43
“Legal and Non-Violent “ in Ethiopia context በሚል ርዕስ እሁድ ሐምሌ 22 ቀን 2004ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በስካይፒ በፕ/ር አለማየሁ ገ/ማርያም አቅራቢነት ውይይት ይካሄዳል ፡፡
Submitted by Admin on Wed, 07/18/2012 - 14:04
በዶ/ር ዳኛቸው እይታ
(ሰንደቅ ጋዜጣ 7ኛ ዓመት ቁጥር 358 ረቡዕ ሐምሌ 11/2004 በዘሪሁን ሙሉጌታ )
Pages